በህይወት ውስጥ የስጠህውን ታገኛለህ ። ሰወችን ለማታለል እና ለማጭበርበር አትሞክር !

ለአንድ ዳቦ ጋጋሪ አንድ ኪሎ ቅቤ የሸጠ አንድ ገበሬ ነበር ። አንድ ቀን ዳቦ ጋጋሪው ትክክለኛውን መጠን ለማግኝት ቅቤውን ለመመዘን ሞከረ። ቅቤው አንድ ኪሎ ሆኖ አላገኘውም። በዚህ ተበሳጭቶ ገበሬውን ወደ ፍርድ ቤት ወሰደው ። ዳኛው ገበሬውን ምን አይነት ሚዛን እየተጠቀመ የቅቤውን ክብደት እንደሚለካ ጠየቀው፡፡ ገበሬው እንዲህ ሲል መለሰ “ክቡር ዳኛ እኔ ባላገር ነኝ ። ትክክለኛ ሚዛን የለኝም" ።ሲል መለሰ
ዳኛው “ታዲያ ቅቤውን እንዴት ይመዝኑታል?” ሲል ጠየቀ ፡ገበሬውም መለሰ፦ “ክቡርነትዎ  ፣  ዳቦ  ጋጋሪው  ቅቤ  ከእኔ  መግዛት  ከመጀመሩ  ከረጅም  ጊዜ  በፊት  አንድ  ኪሎ  ዳቦ  ከእሱ  እገዛ  ነበር  ። ዳቦ  ጋጋሪው  በየቀኑ  ዳቦውን  ሲያመጣ  በመለኪያ  ላይ  አኑሬ  ተመሳሳይ  ክብደት  ያለው  ቅቤ  እሰጠዋለሁ  ፡፡  የሚወቀስ  ካለ እራሱ  ዳቦ  ጋጋሪው  ነው” ሲል መለሰ ፡
  እና ምን ለማለት ነው 
በህይወት ውስጥ የስጠህውን ታገኛለህ ። ሰወችን ለማታለል እና ለማጭበርበር አትሞክር።
Post a Comment (0)
Previous Post Next Post