ከበደ ሚካኤል እንደጻፈው
አንደኛ ፡ ኢትዮጵያዊ የሆንህ ሰው ፡ ሁሉ ፡ ሰንደቅ ፡ ዓላማህ ፡ አገርህና ፡ ነጻነትህ ፣ የሚጠቁበትን ፡ ነገር ፡ ለማስወገድ መይም ፡ ደግሞ ፡ እነሱ የሚጠቀሙበትን ሥራ ለመፈጸም ፡ ብለህ ፤ በሞትህ ጊዜ በሰማይና በምድር ስምህ በወርቅ ፡ ቀለም የሚጻፍበትን የሰማዕትነት ፡ ሥራ በመሥራትህን ፡ ልብህ ፡ ተረድቶት ፡ ደስ ይበለው።ሁለተኛ ፡ አገርን መመውደድ ፡ ማለት ፡ አገርህ ፡ የምትጠቀምበትንና የምትከበርበትን ሥራ መሥራት ነው ።
ሦስተኛ፡አገርህንና ወገንህን ፡ የሚያስንቅ ፡ መይም ፡ የሚጎጻ ፡ ሥራ ፡ ከመሥራት ፡ መሞት ፡ ይሻልሃል ።
አራተኛ ፡ እኛ ፡ ኢትዮጵያውያን የምንሰራው ሥራ መልካም ፡ ቢሆን ፡ ኣግራችን ፡ኢትዮጵያ ፡ እንደምትከበር ፤ የምን ሰራው ሥራ ፡ መጥፎ ፡ ቢሆን ግን እንደምትዋረድ፡ ኣትርሳ ።
አምስተኛ ፡ ኢትዮጵያ አገርህ ፡ ከሌሎቹ ፡ ከማንኛምቹም አገሮች ፡ ሁሉ ይልቅ የምትበልጥብህ ፡ መሆንዋ ፡ ቀንም ፡ ሆነ ፡ ሌሊት በሀሳብህ ፡ ውስጥ ፡ ሳይረሳና ሳይዘነጋ ፡ ተጽፎ ይኑር ።
ስድስተኛ ማንኛውም ፡ የውጭ አገር ፡ ሰው ፡ ለተወለደባት። አገሩ ፡ የሚያስብላት ፡ መልካም ፡ ሀሳብ ወይም የሠራላት፡ መልካም ፡ ሥራ ፡ ሲናገር በሰማህ ወይም ፡ ተጽፎ፡ ባየህ ፡ ጊዜ ኣንተም ደግሞ እንደዚሁ ይህንኑ ያህል ፡ ላገርህ ለኢትዮጵያ ልታስብላትና ፡ ልትሠራላት የሚግባህ መሆኑን ዕወቀሙ ።
ሰባተኛ፡ አንድ ኢትዮጵያዊ ሲበደልና ፡ ሲጠቃ ባየህ ጊዜ የተበደለችውና ፡ የተጠቃችው እናትህ ኢትዮጵያ መሆኗን ተረዳው።
ስምንት፡ ኢትዮጵያ አገርህ በእውነት ትልቅ ሳትሆንና ወንድሞችህ ኢትዮጵያውያን ፡ ሁሉ ሳይደላችው ላንት ብቻህን ፡ የምታግኘሙ ደስታ ገንዘብና ፡ ተድላ በሕልም እንደተገኘ ፡ ወርቅ እና መና ባዶ ሆኖ የሚቀር ፡ መሆኑን ፡ ልብህ ፡ አይዘንጋው ።
ዘጠነኛ፡ ብዙ ገንዘብና ብዙ ርስት ፡ ካገኘ ይልቅ ለአገሩ ፡ ትልቅ ፡ ሥራ ፡ የሠራ ፡ ሰው ፡ ስሙ ፡ ለዘለዓለም ታሪክ ፡ ሲጠራ ፡ ይኖራል ።
አስረኛ፡ ሌሎች ፡ የዓለም ፡ ነገሥታት ፡ ከደረሱበት ፡ የስልጠኔ ፡ ደረጃ ፡ ላይ ፡ አገራችን ፡ ኢትዮጵያ ፡ በቶሎ እንድትደርስ እኛ ፡ ኢትዮጵያውያን ፡ ሁሉ ፡ ማሰብና ፡ መጣጣር ፡ ይገባናል ። ድካማችንና ፡ ትጋታችንም ፡ በተለየ ፡ ለዚሁ ፡ ሀሳብ ፡ ብቻ ፡ እንዲሆን ፡ ያስፈልጋል ።
አስራ አንደኛ፡ በአንድ ፡ ዓመት ፡ ውስጥ ሥስት ፡ መቶ ፡ ስድሳ ፡ አምስት ፡ ቀኖች ፡ አሉ ። በአራት ዓመት ፡ አንድ ዩ ጊዜ ፡ ግን ሦስት፡ መቶ ፡ ስድሳ ፡ ስድስት ፡ ቀኖች ፡ ይሆናሉ ። ይኸውም ፡ የሚሆነው ፡ ጳጉሜ ስድስት ፡ ቀን ፡ በምትውልበት ፡ ዘመን ፡ ነው ።
በአንድ ፡ ዓመት ፡ ውስጥ ፡ አሥራ ፡ ሁለት ፡ ወሮች ፡ አሉ ። እነሱም መስከረም ጥቅምት ሓዳር ታኅሳ ሥ ጥር ፤ የካቲት ፤ መጋቢት ሚያዝያ ግንቦት ፣ ሰኔ ፤ ሐምሌ ፤ ነሐሴ ናቸው።
በሦስቱ ፡ ዓመት ፡ አምስት ቀን ፤ በአራተኛው ኣንድ ፡ ጊዜ ፡ ስድስት ፡ ቀን ፡ የምትሆን ፡ ጳጉሜ አለች ።
በአንድ ፡ ዓመት ውስጥ : አምሳ ሁለት ሳምንቶች አሉ። በአንድ ፡ ሳምንት ፡ ውስጥ ሰባት ቀናቶች አሉ ። እነሱም ፦ ሰኞ ፤ ማክሰኞ ፡ ረቡዕ ፤ ኅሙስ፣ አርብ ፣ ቅዳሜ እና እሁድ ናቸው።
የዓመቱ ወሮች ፡ በአራት : ክፍል ይከፈላሉ ። እነሱም ጥቢ፣ በጋ ፣ በልግ እና ክረምት ናቸው።
*
እግዚአብሄርን መፍራት የጥበብ ሁሉ መጀመሪያ ነው።
*
ከማዘዝ በፊት አስቀድሞ መታዘዝን ማወቅ ያስፈልጋል።
*
ጥሩም ነገር ቢሆን ከመጠን ካለፈ ሁልጊዜ መጥፎ ነው።
*
ተቢት እና ውርደት አካል እና ጥላ ናቸው ሳይለያዩ ሁልጊዜ ቀዳሚ እና ተከታይ ሁነው
ይኖራሉ።
*
እህል እና ውሀ ሰውነትን እንደሚመግቡት ሁሉ መጽሀፍትን ማንበብ እንደዚሁ መንፈስን
ይመግባል።
*
ከበላይህ ያሉትን ሰወች እያየህ ልብህ ቅናት አይደርበት ። ይልቅስ ካንተ በታች
ያሉትን ችግርተኞች እየተመለከትክ እድልህ ከነሱ የተቻለ በመሆኑ ፈጣሪህን እመስግን።
*
ማንም ሰው ቢሆን መከራ ወድቆበት ባየህ ጊዜ አትፍረድበት ። ወይም አትጨክንበት
። በእሱ ላይ የደረሰ መከራ ምናልባት ባንተም ላይ ወደፊት ሳይደርስብህ
አይቀርም።
*
ምንም እንኳ የሚያስመሰግንህ ትልቅ ስራ ብሰራ ምንጊዜም ቢሆን አትመካበት። ትምክህት ማንኛውንም ዋጋ ቢሆን ያቀለዋል። ትህትና ኝ ከሁሉ ሙያ የበለጠ ዋጋ ያለው ባህሪ ነው።
*
የፈረንሳዩ ፈላስፋ እንዲህ ይላል፡ ቃል ለሰው ልጅ የተሰጠው ሀሳቡን እንዲገትጽበት ነው ይባላል። ነገር ኝ ሀሰት ነው። ቃል ለሰው ልጅ የተሰጠው በዋናነት ሀሳቡን እንዲሸፍንበት ነው።*
ሰው በህይወቱ ሲኖር የሚያገኘው መልካም ነገር ሁሉ የሚቀበለው ከተወለደበት አገር ስለሆነ አስፈላጊ ምክኒያት በመጣ ጊዜ ያለውን መልካም ነገር ሁሉ ህይወቱን እንኳ ሳይቀር ሳያመነታ ላገሩ ሲ፤ል ለሰዋ ይገበዋል።
*
እንድ ፡ ትልቅ ፡ ሊቁ ፡ ስለ ፡ ስንፍና ፡ መጥፎነት ፡ ሲናገር እንዲህ ፡ አለ “ ማናቸውንም ፡ ዐይነት' ጥፋት ፡ ያጠፋ ፡ ሰው , ሁሉ ፡ ይቅርታ ፡ ሲደረግለት' የተገባ ፡ ነው ። ምሕረት ፡ ሊደረግ ለት፡ የማይግባ ፡ አንድ፡ ብቻ ፡ አለ ፡ እሱም ሰነፍ ሰው ነው።
*
ከጥንት፡ ጀምሮ ፡ ሲነገር ፡ የሚኖር፡አንድ፡ የላቲን ፡ተረት፡ እንዲህ ይላል " ጦርነት እንዳይመጣብህ ፡ ብትፈልግ ሁልጊዜ' ለጦርነት' የተሰናዳህ ፡ ሆነህ ፡ መቀመጥ ይገባሀል ።
*
በጌታና በድኻ ፡ ሰው ፡ መካከል ' የሚገኘው ልዩነት በጣም ፡ የተራራቀ ፡ ነው ይሁን ፡ እንጂ ፡ ጌትነትና፡ ድኽነት ጐን ለጐን ሲሄዱ ፡ ይኖራሉ ።
*
ጸሀይ ጠዋት ጠዋት የምትወጣው የሱን ድምጽ ሰምታ ' እየመሰለው ፡ በልቡ የሚኮራ አንድ አውራ ዶሮ ነበር ይባላል። በሰወችም መካከል ለሰሩት የማይችሉትን ስራ የሰሩ እየመሰላቸ የሚኩራሩ ፣ ሲመኩ የሚታዩ ሰወች ይገኛሉ።
*
ምቀኛ ሰው የክፋቱ ብዛት የሞቱ ሰአት በደረሰች ጊዜ እኔ ከሞትኩኝ በኋላ አለም ጨለማ ሁና ትቅር ብሎ በማሰብ የሚቻለው ቦሆን ኖሮ ጸሀይን አጥፍቷት ለመሞት በወደደ ነበር። ቅን ሰው ኝ ለአለም የሚጠቅም ስራ ለመስራት ሲል ህይወቱን ይሰዋል።
*
የሰው ሙያ ሦስት ፡ ዐይነት ፡ ነው ። አንደኛው ፡ ማሰብን ማወቅ ሁለተኛው ፡ መናገርን ፡ ማወቅ ፡ ሦስተኛው መሥራትን ማወቅ ።| አብዛኞቹ ፡ ብልሆች ፡ የሚባሉ ሰዎች ፡ ከእነዚህ ከሦ ስቱ አንደኛውን ' ብቻ : ነው ፡ የሚይዙ። ወይም ፡ መሥራት ፣ ያውቁና ፡ ትክክል ፡ ማሰብ ፡ አይችሉ ፡ ይሆናል ። ስለዚህ ትክክል ካለማሰባቸው ፡ የተነሣ ፡ ደክመው ፡ የሠሩት ፡ ሥራ ፡ ሁሉ ፡ ይፈርሳል ። ወይም ፡ ደግሞ ፡ ንግግር ፡ አሳማሪዎች ፡ ዐሳባቸውና ፡ ሥራቸው ብላሽ ይሆናል ። ትክክል ፡ ዐስቦ : ያሰበውን ትክ ክል ፡ አድርጎ ፡ በቃል ፤ ወይም ፡ በጽሕፈት ፡ አስረድቶ ፡ እንዳሰበውና ፡ እንደተናገረውም ፡ አድርጎ ' ትክክል ፡ የሚሠራ ፡ ሰው ፡ እውነት ፡ ትልቅ ፡ ዐዋቂ ፡ ነው ሊባል ይቻላል ።
*
ዶስታ ፡ ምንድን ፡ ነው'ብለው ፡ ቢጠይቁት ፡ አንዱ ፡ ሊቅ ፡ ደስታ ፡ ማለት ፡ ጤንነት ፡ ነው ፡ ብሎ ፡ ተናገረ። ጤንነትሳ፡ደግሞ፡ ምንድን ፡ ነው ፡ብለው መልሰው ፡ ቢጠይቁት ፤ ጤንነት፡ ማለት፡ ሁሉም ፡ ነው ፡ ብሎ ፡ መለሰ ። እውነት ፡ ነው ፡ ጤንነት፡ ከሌለ ፡ ሁሉ ፡ ነገር ፡ ከንቱ ፡ ነው ። ጤንነት ፡ ካለ ፡ ግን ፡ ሁሉም ፡ ነገር ፡ መገኘቱ ፡ አይቀርም ።
*
በዓለም ፡ ላይ ፡ ትልቅ ፡ ሥራ ፡ ለመሥራት ፡ የሚቻለው ሠሪው ፡ ሰውና ፡ ለመሥራት፡ የተመቸበት ፡ ጊዜ ፡ እነዚህ ሁለቱ : ሲገናኙ ፡ ነው ። ትልቁን ፡ ሥራ ለመሥራት ፡ የሚችለው ፡ ሰው ፡ ባልተመቸ ፡ ጊዜ ፡ ሲፈጠር ሊሠራው ፡ የሚችለውን ፡ ሥራ፡ሳይሠራው ፡ መቅረት ፡ ግድ፡ ይሆንበታል ። ልሥራም ፡ ቢል ጊዜው: አይደለምና ፡ አይሆንለትም ። ትልቅ ፡ ሥራ ለመሥራት፡የተመቸ፡ በሆነበት፡ ጊዜ ፡ ደግሞ ፡ ሊሠራው ፡ የሚችል ፡ ሰው ፡ ባለመፈጠሩ፡ መልካሙ ፡ ጊዜ በከንቱ ፡ ያልፋል ። እነዚህም፡ ሁለቱ፡ተፈላላጊ ነገሮች፡የሚገናኙት በብዙ፡ ዘመን ፡ ውስጥ፡ ጥቂት፡ጊዜ ነው ።