ዓይነ ስውር መሆኗን ሙሉ በሙሉ የምትጠላ አንዲት ዓይነ ስውር ልጅ ነበረች። የሚወዳት እና ምን ጊዜም ከጎኗ የማይለያት ፍቅረኛ ነበራት። ሁል ጊዜ ያስባላት ነበር። እናም አንድ ቀን አይኗ ማየት ከቻለ እንደምታገባው ቃል ገብታለት ነበር።
አንድ
ቀን አንድ ሰው አንድ ጥንድ ዓይኖቹን ሰጣት
። አሁን ፍቅረኛዋን ጨምሮ ሁሉንም ነገር ማየት ቻለች ። ፍቅረኛዋ፣ “አሁን ሁሉንም ነገር ማየት
ቻልሽ። ታገቢኛለሽ?”
ሲል ጠየቃት።
ልጅቷም
ፍቅረኛዋ ዓይነ ስውር መሆኑን ስታውቅ ደነገጠች እና ልታገባው አልፈለገችም። የወንድ ጓደኛዋ እያለቀሰ ደብዳቤ ጻፈላት፡-
“አይኖቼን ብቻ ተንከባከቢልኝ ውዴ”
ከታሪኩ ምን እንማራለን ?
ሁኔታችን
ሲቀየር አእምሯችንም ይለወጣል። አንዳንድ ሰዎች የቀድሞው ማንነታቸው ለአሁን ሁኔታቸውን መሰረት
መሆኑን መገንዘብ ሲሳናቸው እናስተውላለን።